እኔ የምለው! አባባሎቻችንን ወይም ሥነቃሎቻችንን ማን ነው ግን የሚፈጥራቸው? በጣም እኮ የሚገርም ነገር ነው፡፡
አንድ እኮ አይስቱም! ለምሳሌ፦ በርእስ የጠቀስኩትን እንይ “እግዚአብሔር ማልቀስ ሲያምረው ጎጃሜን ይገላል፤ መሳቅ ሲያምረው ደግሞ ትግሬን ያጠግባል!” ይባላል፡፡ አሁን እግዚአብሔር የሚስቅና የሚያለቅስ ሆኖ አይደለም እንዲህ መባሉ፡፡ ነገር ግን ጎጃሞች ሐዘናቸው መረር ስለሚል፣ ለቅሷቸው አንጀት ስለሚበላና ሙሾ ባወረዱ ጊዜ “እንባ ደረቅ፣ አረመኔ!” የተባለን ሰው እንኳ ሳይቀር በለቅሶ የሚያንፈቀፍቁ በመሆኑ፤ ትግሬ ሲጠግብ ደግሞ የሚሠሩትን ከማጣታቸው የተነሣ በጣም የሚገርም፣ ሆድ አስይዞ በሳቅ የሚያንፈረፍርና ፈጽሞ የማይጠበቅ ነገር ማድረጋቸውን በአጽንኦት ለመግለጥ ነው እንዲያ መባሉ፡፡
ይህች ጥጋብ የምትባል ነገር የስንት ነገር መለኪያ መሣሪያ ናት መሰለቻቹህ! አንድ ሕዝብ ወይም ኅብረተሰብ በሳል፣ አስተዋይ፣ ብልህ፣ አዋቂ፣ የተረጋጋ ሰብእና የያዘ፣ ጨዋ፣ ባለ አእምሮ፣ በራስ መተማመን ያለው ነው የሚያሰኘው ጥጋብን የቻለ፣ ጥጋብ እሚሠራውን የማያሳጣው እንደሆነ ነው፡፡ እንዲህ የሆነ ኅብረተሰብ በጣም የበሰለ፣ ክብርና ኩራት ያለው፣ የጠለቀ ወይም ስር የያዘ በሳል የሕይዎት ምልከታ ፍልስፍና እምነትና ሥልጣኔ ያለው፣ ከፍ ያለ የሞራል (የቅስም) ልዕልና ያለው፣ ከሕይወት ተሞክሮው ብዙ የተማረ ጥንታዊ ማኅበረሰብ መሆንያረጋግጣል፡፡
በእርግጥ ከዚህ ቀደም ከላይ የጠቀስኩላቹህን አባባል ትክክለኛነት የሚያረጋግጡ በርካታ ነገሮች ያጋጠሙኝ ቢሆንም በቀደም ቅዳሜ ምሽት (የካቲት 11,2009ዓ.ም.) ታዲያስ አዲስ በተባለ የሸገር ራዲዮ (ነጋሪተወግ) የመዝናኛ ዝግጅት ላይ የሰማሁትም ቀላል አላስገረመኝም፡፡ አንዱ ነው አሉ (ስሜ አይጠቀስ ብሏል ተብሎ ስሙ አልተጠቀሰም) አዲስ ከወጣው የኤደን ገ/ሥላሴ የዘፈን አልበም (ጥራዝ) ውስጥ “አንደኛው ዘፈን ከሕይዎቴ ጋር ስለተገናኘ አስደሰተኝ!” ብሎ በዚህች ዘፈን የተነሣ አንዷን የዘፈን አልበም (ጥራዝ) በ50ሽህ ብር እንደገዛ “የምሽቱ የመዝናኛ ዜና!” ብለው አወሩልን፡፡
አይገርምም? አይደንቅም? በዚህ ሀገሪቱ ስንት ሚሊዮን (አእላፋት) ዜጎች ተርበው ስቃይ ላይ ባሉበት ወቅት!፣ በኑሮ ውድነት የተነሣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በችጋር እየተጠበሰ ኑሮ እንደ እሬት ምርርርርር ባለው ሰዓት! እንዴት ያለ ጥጋብ ቢሆን ነው እንዲህ ዓይነት ነገር የሚያስፈጽም?
ደሞ ምንአለ ጥጋባቸውን ሳናይ ሳንሰማባቸው እዛው በየቤታቸው ቢያስቀሩት? የንቀታቸው ንቀት ዓይተንና ሰምተንእንድንቃጠል እንድንጨስ የጥጋብ ድርጊታቸውን በአደባባይ ያደርጉታል! ለነገሩ የጥጋብ አንዱ መገለጫው ይሄ አይደል? ቦታና ሰዓት ሳያስለይ ማጨማለቅ! የመረጃ ጉዳይ ይሆናል እንጅ እርግጠኛ ነኝ ከዚህ የከበደ ብዙ ለማመን የሚያዳግት “ጉድ!” የሚያሰኝ ነገር የምታውቁ በርካቶች ትኖራላቹህ፡፡ ከኛ ሰፈርም አንድ ትግሬ አለ ልጁን በርቀት መቆጣጠሪያ (ሪሞት ኮንትሮል) በምትሽከረከር የአሻንጉሊት መኪና (ተሽከርካሪ) አስቀምጦ ሰፊ ግቢው አልበቃ ብሎት ከግቢ ውጭ እየተወነነ ሲያንሸራሽረው የማየው፡፡ ከዚህ ሰው ቤት ከሚወጣ ቆሻሻ ላይ እያነሡ የየዕለት ምግባቸውን የሚመገቡ ልጆች አሉ፡፡ እነሡ ሳይፈታትሹት የቆሻሻ ከረጢቱን ለቆሻሻ አንሺዎች አያስነሡም፡፡
ብቻ ጥጋብን በተመለከተ እያንዳንዱን የማውቀውን ትግሬ ተረቱን በሚያረጋግጥ መልኩ ያልታዘብኩት የለም፡፡
ኧረ ተዉ! ተዉ! ተዉ! ተዉ! አስቡ! አስተውሉ! እግዚአብሔርን፣ ግፍንና ጡርን ፍሩ!፣ የደሀ ድሀ ወይም ከድህነት ወለል በታች የሆነ ሕዝብ ባላት ሀገር ኢትዮጵያ ውስጥ መሆናቹህን አስቡና ጥጋባቹህን በልክ አድርጉት?
ሠርቶ ንጹሕ ላቡን ጠብ አድርጎ ያገኘ ሰው እንኳን በንጹሕ ገንዘቡ ለሚያደርገው የሰው ዓይን የሚያስገባ ነገር ለማድረግ ይሳቀቃል! በዚህ ሕዝብ ላይ ለመኩራራት በፍጹም አይደፍርም! እናንተ ሀገረንና ይሄን ድሀ ሕዝብ ገፍፋቹህ! ዘርፋቹህ! በምታካብቱት የግፍ ገንዘብ እንዲህ ባጠገባቹህ ምስኪን ሕዝብ አናት ላይ ትቀዝኑበታላቹህ? ምን ያህል የሞራል (የቅስም) ድሀና ገለባ ብትሆኑ ነው እንዲያው ጥቂትም እንኳ መሳቀቅና ሐፍረት የሚባል ነገር የማይታይባቹህ???
እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ!!! ሰአሊ ለነ ቅድስት!!!
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው