ሰሜን ጎንደር

በሰሜን ጎንደር 8 ቀበሌዎች ውስጥ በቅማንት አስተዳደር ስር ለመጠቃለል ወይንም በነበረው አስተዳደር ስር ለመቀጠል ሕዝበ ውሳኔ መካሄዱን ተከትሎ ዛሬ ውጤቱ በፌዴሬሽን ምክር ቤት ፀድቋል።

በዚህም መሰረት 7 ቀበሌዎች በነበረው አስተዳደር ስር ለመጠቃለል ሲወስኑ 1 ቀበሌ ደግሞ በቅማንት አስተዳደር ሥር ለመጠቃለል ውሳኔ አስተላልፈዋል።

በፌደሬሽን ምክር ቤት የህዝብ ግኑኝነት እና ኮሚኒኬሸን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ገብሩ ገ/ስላሴ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ውሳኔውን የተመለከተው የፌደሬሽን ምክር ቤት ዛሬ ውጤቱን በሙሉ ድምፅ አጽድቆታል።

Source   –   BBC/Amharic