november 13, 2017 12:01

በሠራዊቱ ውስጥ የቅርብ ሰው የሆነ ግለሰብ የተናገረው እንደወረደ ወዲህ አመጣሁት

” እኔ በሠራዊቱ ውስጥ ለ7 አመታት ቆይቻለሁ በብዙ ግንባሮች ነበርኩ ከየትኛውም ጊዜ በላይ ለወያኔዎች ከባድ ወቅት ይህ

አመት ሆኖባቸዋል፡፡

ድንገት ሳይታሰብ የመጣ የለውጥ ንፋስ አስደንግጧቸዋል ከስብሰባ እሰከ ግምገማ ቢሮጡ ያው ሆኗል፡፡

የህዝቡ ጠንካራ ተቃውሞ ውስጡንም በትኖታል::

አሁን ላይ በእርግጠኝነት መናገር የሚቻለው ስርዓቱ አመቱን በሰላም መጨረስ አይችልም፡፡

ትንሽ የመግዣ ጊዜ ከተሳካላቸው በእነሱ ጥንካሬ ሳይሆን በሌሎች ድከመት ይሆናል፡፡

አመራሩም ራሱን ከውድቀት ለመታደግ አልቻለም ሁሉ ነገር አልቆበታል የአቅም እና የስነ ልቦና ዝግጅት ዛሬ በወታደሩ ዘንድ የለም፡፡

በመከላኪያ ውስጥ ኀይል አሰላለፉ ከወትሮ በከፋ ተዘባርቋል፡፡ ..

ማን መሪ? .. ማን ተመሪ እንደሆነ እንኳ ለመለየት ይከብዳል፡፡

በዝቅተኛ እርከን የሚገኙ የሠራዊቱ አባሎች በተለይ የኦሮሞ ወጣቶች ሱማሌ ሌላውም አብዛኞቹ እየጠፉ በመሸሽ ላይ ናቸው፡፡

አዲስ ምልምል ለመመዝገብ በተደጋጋሚ ቢሞከር ከአቅም በላይ አድርጎታል፡፡ ውስጡ ሲፈተሽ የሀገር መከላኪያ ሠራዊት

የምትለው ተቋም አይደለም፡፡

by ሳተናው