ህዳር 30 ቀን 2010 ዓ.ም.

(December 13, 2017)

በሰሞኑ በወልድያ ከተማ የትግራይ እግር ኳስ ቡድን ከወሎ ቡድን ጋር ሊያደርግ የነበረውን ጨዋታ ተከትሎ የተነሳው ብጥብጥ ለአያሌ ሰዎች ህይወት መጥፋትና መቁሰል ለብዙ ንብረት መውደምም ምክንያት ሆኗል።ይህ እስፖርትን ሽፋን አድርጎ በወያኔ ዘበኛ ፈጥኖ-ደራሽ ሃይል ታጅቦ ወደ ቦታው የተላከ የጥፋት ሃይል ገና ከወሎ ድንበር ላይ ሲደርስ ጀምሮ የሕዝቡን ስሜትና ሞራል የሚነካ ፍጹም ብልግናና ድፍረት የተሞላበት የዘር ጥላቻን ያዘለ ስድብና ህገ ወጥ የቁጣ-ቅስቀሳ ተግባር (provocation) እንጂ በእለቱ የተፈጸመ ድንገተኛ ክስተት አልነበረም።

የዘር በሽታ ያሳበዳቸው እነዚህ የጥፋት መልእክተኞች በስካር መንፈስ በሚመስል ማጭበርበር የፈጸሙት ወንጀል ተዘጋጅተውና ሰልጥነውበት የመጡበት እንጂ በቦታው የተከሰተ አጋጣሚ አይደለም። በሌሎች ክልሎችም ተመሳሳይ ድርጊቶችን መንግስት ተብዬው በመፈፀም ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ ሕዝብ ተገንዝቦታል። ለመሆኑም የጠብ ቀስቃሹን ብልግና ተከትሎ ለሚነሳው ህዝባዊ ንዴትና ቁጣ መልስ እንዲሰጥ ተዘጋጅቶ የተላከው የታጠቀ የአጋዚ ሃይል ጭብጥ ማስረጃ ነው።

ይህንንም ተከትሎ የትግሬ ነጻ አውጪ ነኝ ባዩ ወያኔ መጀመሪያዉኑ እንዳሰበዉ ወጣቶችን በጅምላ በማፈስ ትግራይ ዉስጥ በተዘጋጀ የጅምላ ማጎሪያ በሌሊት እያደኑ በመያዝ በማጎር ላይ ይገኛሉ። በዚህ ካምፕ ዉስጥ የሚደርስባቸዉን ስቃይና እንግልት መገመት አያዳግትም። አካባቢዉን አስተዳድራለሁ የሚለዉ ደካማ ተለጣፊ ድርጅት ይህ ሁሉ ዉንብድና ሲፈፀም ዝም ብሎ ከመመልከት በቀር የወሰደዉ ምንም አይነት እርምጃ የለም።

ከወልቃይት ጠገዴ በተጨማሪ ትግራይ ውስጥ በሚኖሩ የትግራይ ተወላጅ ባልሆኑት ኢትዮጵያውያን ላይ የሚፈጸመው ጥቃት ቀጥሏል። የንግድ ድርጅቶች በእሳት ጋይተዋል፣ሰዎች እየተደበደቡ በከፍተኛ ደረጃ ቆስለዋል፤ የዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ላይም እንዲሁ ከባድ ጉዳት ደርሶ የሞቱም እንዳሉ ይሰማል።ሌሎቹም መግቢያ መውጫው ጠፍቷቸው በመከራ ዉስጥ ናቸው።

በጥላቻና በዘረኝነት ማጥና መቀመቅ ውስጥ የተዘፈቀው ወያኔ ላለፉት 27 አመታት በወሎ ላይ መጠነ ሰፊ ዝርፊያ፣ ግድያ፣ ማፈናቀል፣ ማደህየት እና የመሳሰሉትን ዘርፈ-ብዙ ጥፋቶች አድርሷል፤እያደረሰም ይገኛል። ለአብነት ለመጥቀስ ያህል፦

«ወሎ የኢትዮጵያ ዉርስና ቅርስ ማኅበር» ለዚህ በአንድ አናሳ ጎሳ ላይ ተመርኩዞና በሆዳም ግብረ-ኣበሮቹ ተደግፎ በወሎ ላይና በመላዉ ኢትዮጵያ ላይ እያደረሰ ያለዉን ግፍ በአስቸኳይ አቁሞ ከቻለ ከህዝብ ጋር ታርቆ ካልቻለ ግን ስልጣኑንን ለህዝብ እስካላስረከበ ድረስ ሁሉንም ህጋዊና ፍትሀዊ መንገዶችን በመከተል ህዝባችንን የምናነቃና የምናታግል መሆኑን እየገለፅን። በተለይም በትግራይ የማጎሪያ ካምፕ ዉስጥብ ሆነ በየወህኒ ቤቶች በመሰቃየት ላይ የሚገኙትን ወጣቶችና የፖለቲካ እስረኞች ያለምንም ቅድመ-ሁኔታ እስካለቀቀ ድረስ ህዝባችን ፍርሃትን ስላሽነፈ ትግሉን እንደማያቆም ግልፅ እየሆነ መምጣቱን ልናስገነዝብ እንወዳለን።

ለሌሎች የኢትዮጵያዉያን የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ሲቪክ ማህበራትና የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችን ደግሞ ልዩነቶቻችንን በማጥበብ፣ ሰጥቶ በመቀበል መርህ በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ በመቀመጥ ሁላችንም እንወክለዋለን ለምንለዉ ድርጅትም ይሁን ክፍለ-ሃገር የአገርህን-አድን የጋራ ግንባር በመፍጠር ላለፉት ሩብ ምእተ-አመት በህዘባችን ጫንቃ ላይ ተፈናጦ ይህንን ሁሉ ግፍ በማድረስ ላይ የሚገኜዉን እብሪተኛ የታሪክ አተላ የሆነ ቡድንን ፍፁም በቃህ ልንለዉ ይገባል እንላለን። ይቻላልም።

በኢትዮጵያ የውስጥ ጠላቶች ያሰፈኑት የጭቆና ዘመን እያከተመ ነው። በዚህ አጋጣሚ ለሌሎች ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ልንገልፅና ልናሰምር የምንወደዉ ነገር ቢኖር የብዙ ነገዶች ድርና ማግ የሆነው የወሎ ህዝብ እንደ ቀድሞ እንደታሪኩ ለሀገሩ ነፃ መዉጣት የበኩሉን አስተዋፅኦ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ነው። በተለይም ጎበዝ-አለቆቹን ታድጎ ሁለግብና (የኢኮኖሚ ማእቀብም ጭምር) መጠነ-ሰፊ የትግል ስልቶችን መንደፍ ለሰብዓዊና ለሲቭላዊ መብቶች ለሚደረገው የእምቢተኝነት ትግል ቁልፍነቱን ሕዝባችን እየተገነዘበ መምጣቱ ያኮራናል።

ያሸባሪዎችና የወሮበሎች ስርዓት በሕዝብ ትግል ያከትማል!

የጎሳ ካርድህን ቀደህ የዶግ አመድ አድርገው!

ኢትዮጵያ ለብዙ ዘመናት ከባድ ፈተናዎችን ያለፈች ሉዓላዊ አገር ናት!

ድል ለወሎና ለሰፊዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ!!

=====

Wollo.org        “ወሎየነት መለያችን፥ ኢትዮጵያዊነት ማንነታችን”