ክፍል አንድ

ህወሓት የጦር አበጋዞች መንግሥት TPLF WARLORDS STATE የወያኔ ፋሽስታዊ ‹የአስቸኮይ ጊዜ አዋጅ!› ይነሳ!!! ያለ ኢኮኖሚ ነፃነት የፖለቲካ ነፃነት የለም!!!

ለኢትዮጵያ ሃገራዊ ንቅናቄ፣

ለኢትዮጵያዊያን የጋራ ግበረ ኃይል፣

ለኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ፣

ለኢትዮጵያውያን ተጋሩ፣

ለሁሉም ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶችና የሲቪክ ማህበራቶች፡-

የህወሓት/ ኢህአዴግ ፋሽስታዊ መንግሥት ለሦስተኛ ጊዜ የአስቸኮይ ጊዜ አዋጅ አውጆል፡፡ ወያኔ የተነቃነቀ በትረሥልጣኑን ለማስጠበቅ በአዋጅ ህዝብ ለመግደል ቆርጦ ተነስቶል፡፡ ወያኔ በሃገሪቱ የተቀጣጠለውን ህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ትግል ለማፈንና ህዝብን በተለይ ወጣቶችን ለመግደልና ለማሰር ዳግም ከበሮውን ጎስሞ፣ እንቢልታውን ነፍቶ፣ የአስቸኮይ ጊዜ አዋጅ አውጆል፡፡ ወያኔ የነፋስ ግቢ፣ ነፍስ ውጪ የመጨረሻ ቱልቱላ አዋጁን አውጆል፡፡ ወያኔ መንግሥታዊ የመጨቆኛ ማሳሪያዎቹን ካራ ስሎ፣ የእስር ቤት በረቱን ከፍቶ፣ የህዝብ ልጆችን ለመግደል ዝናር ጥይቱን ታጥቆ ተኩሶ ለመግደል ዝግጅቱን አጠናቆል፡፡ ማሃይሙ ወያኔ ያልገባው ነገር የሃገሪቱ ኢኮኖሚ ከሞተ በኃላ፣ በሙስናና የኮንትሮባንድ ንግድ ሰክሮ እግሮቹን ከበላ በኃላ፣ የውጪ ንግድ ገቢውን ወርቁን፣ ሠሊጡን፣ የቁም እንሰሳቱን፣ ጫቱን ወዘተ ሸጦ ከጨረሰ በኃላ፣ የውጪ ምንዛሪ ንዋይ ዶላርና ፓውንድ ባህር ማዶ አገራቶች አግዞ ከጨረሰ በኃላ አገሪቱን ኢኮኖሚ አንኮታኩቶ ከጣለ በኃላ አሁንስ በቃ ብሎ የተነሳን የኦሮሞ ቄሮ ህዝባዊ እንቢተኝነት፣ የአማራ ፋኖዎች ተጋድሎ፣ የደቡብ አቦሸማኔዎች አመፅ፣ ወደ ሰሜን አናብስቶች እየተቀጣጠለ ባለበት ወቅት የአስቸኮይ ጊዜ አዋጅ ከምን ሊያስጥለው!!!   ድመቱ ወያኔ ስልጣኑን እንደ ግልገል ድመት ልጆቾን በጥርሱ ነክሶ አንዴ ለመለስ ዜናዊ፣ አንዴ ለኃይለማሪያም፣ አንዴ ለሽፈራሁ ሽጉጤ፣ አንዴ ለደብረጺዩን ቢሾምና ቢሽር ኢኮኖሚውን አያቃናውም፣ የተንሸራተተውም ጎማ መያዥያና መጨበጫ ፍሬን የለውም፡፡ የወያኔ ሥልጣን እንደ ጉም በኖል፣ ህወሓት እራሱን ኢህአዴግን ሊያስተዳድር ያልቻለ መንግሥት ሆኖል፡፡ በሃያ አንደኛው የሠለጠነ ክፍለ ዘመን፣ ችግሮች በጠረጴዛ ዙሪያ በውይይት በሚፈቱበት ዘመን፣ ቂሎ ማሞ ህወሓት ቂልነቱን ያሳያል፣ በወደቀው ኢኮኖሚ ላይ አዋጅ ቸለሰበት፡፡ መንግሥታዊ ነጭ ሽብሩን የዓለም ቱሪስቶች መጥተው እንዲያዩለት፡፡ የአፍሪካ ህብረት፣ የአውሮፓ ኢኮኖሚክ ኮሚሽንና ልዩ ልዩ ሃገራቶች ኢንባሲዎችና ዲፕሎማቶች ጋብዞል፣ ትያትሩን ለማሳየት፡፡ የሞቱ ጅቦችን አህዬች አይፈሩም!!!

የህወሓት/ ኢህአዴግ ፋሽስታዊ መንግሥት የአጋዚ ጦር መንግሥታዊ ነጭ ሽብር ቀጥሎል፣ አጋዚ ጦር በጨለንቆ፣ ወልዲያ፣ ቆቦ፣ መርሳ፣ ሃማሬሳ፣ በደብረዘይት፣ ዉልቂጤ፣ በሻሸመኔ፣ ወዘተ ህዝብ እየጨረሰ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያዊያንን ህዝባዊ ትግል በጠመንጃ አፈሙዝ ለማፈን ግን ጭራሽ አይቻለውም፡፡ ፋሽታዊው የአጋዚ ጦር  ነፍሰበላ ወንጀለኞች ለፍርድ ይቅረቡ፣ ይህንን ህዝባዊ ትግል ከዳር ለማድረስ ሃገር አቀፍ ብሄራዊ ትግል ግድ ይላል፣ ትግሉን የምትመሩ ድርጅቶች ህዝቡ ሠልፍ ሳይወጣ፣

  • አንደኛ/ የቤት ውስጥ መቀመጥ አድማ በማድረግ፣
  • ሁለተኛ/ ኢትዩቴሌኮምን ያለመጠቀም አድማ፣ የትግል ሥልት በመጠቀም የወያኔን የገንዘብ ምንጭ መዝጋትና ኢኮኖሚውን ማድቀቅ
  • ሦስተኛ/ የኡኡታና የፊሽካ የትግል ሥልት በአንድ ለሊትና ሰዓት የኡኡታ፣ ጡሩንባና የፊሽካ ጩህት የማሰማት አድማ ማድረግ በተለይ የአፍሪካ ህብረት፣ወይም የአውሮፓ ህብረት ስብሰባ በአዲስ አበባ መዲና በሚደረግ ወቅት
  • አራት/ ለትግራይ ህዝብ ጥሪ ማድረግ፣ በተለይም የትግራይ ወጣቶችን የትግላችን አጋር በማድረግ ህወሓት/ወያኔን ከትግራይ ህዝብ በመነጠል ወደ ብሄራዊው ትግል መሳብ ወያኔ በስብዓዊ ጋሻነት የትግራይን ህዝብ አግቶታል፣ ህዝባዊው ትግል ይሄን መሥበር መቻል አለበት፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ጠላት ወያኔ ሥርዓት እንጅ የትግራይ ህዝብ እንዳልሆነ ማሳየት የኦሮሞ፣ የአማራ፣ የትግራይ፣ ጋምቤል፣ አፋር፣ የደቡብ ወዘተ ወጣቶች ብሄራዊ ትግል ማቀናጀት ለድል ያበቃል፡፡
  • አምስተኛ/ በባህር ማዶ የሚኖሩ ኢትዮጵያውን ድምጻቸውን ከመቼውም ጊዜ በላይ ለዓለም ህብረተሰብ ማሰማትና የወያኔ የውጪ ምንዛሪ ማግኛ የሆነውን የሃዋላ መላክ አድማ በማጠናከር የወያኔን የገቢ ምንጭን ከእንጥሉ ላይ ማድረቅ
  • ስድስተኛ/ ሌሎች ልዩ ልዩ የትግል ስልቶችና የኢኮኖሚ ማዕቀቦች በወያኔ ሥርዐት ላይ በማድረግ መታገል ይኖርብናል፡፡

አሁንም የቀሩት የህሊና እስረኞች፣ የኢትዩጵያ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ እነ አንዳርጋቸው ጽጌና፣ የግንቦት 7 የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ!!!   ተፅዕኖ ለማድረግ ትግሉን መቀጠል ይኖርብናል፡፡ ይህንንም የህብረት የትግል ጥሪ የኢትዩጵዊያን ድረ-ገፆች፣ የኢትዩጵያ ሣተላይት ቴሌቪዥን (ኢሣት)፣ ኦሮሚያ ሚድያ ኔትወርክ፣ ቄሮ የኦሮሞ ወጣቶች አስተባባሪ፣ ፋኖ የአማራ ወጣቶች አስተባባሪ፣ የማህበራዊ ድረ-ገፆች አክቲቪስቶች/ጦማሪዎች (በፋስቡክ፣ ቲውተር፣ ወዘተ) በልዩ ልዩ መገኛኛ አውታሮች ወዘተ በኢትዩጵያ የህሊና እስረኞች እንዲፈቱና በህወኃት እስርቤቶች ውስጥ የሚደረጉ ኢሰብዓዊ ግርፋትና የወሲብ ጥቃትን ለዓለም ህብረተሰብ ለማጋለጥ የወያኔ መንግሥት የጣለው የአስቸኮይ ጊዜ አዋጅ እንዲያነሳ መታገል፣ ለዓለም ህብረተሰብ ወያኔን በማጋለጥ የሚደረግ ህዝባዊ ብሄራዊ የአድማ ጥሪ እንዲደረግ የማስተባበርና የአድማውን ቀን የመቁረጥ አስፈላጊ መሆኑን እናሳስባለን፡፡ ህዝባዊውን ትግል እንድትመሩ ህዝብ ይጠይቃል፡፡ ክብር  ለተሠው ኢትዮጵያውያን ሠማዕታት ይሁን!!!  የህወሓት አጋዚ ጦር ሠራዊት ለፍርድ ይቀርባል!!! በአንድ ላይ በህብረት እንነሳ!!!  የኢትዩጵያ መከላከያ ሠራዊት አፈሙዝህን ወደ ወያኔ አዙር!!!  የህሊና እስረኞች ይፈቱ!!!   በወያኔ እስር ቤቶች ውስጥ ኢስብዓዊ ግርፋትና ማሰቃየት ይቁም!!!

በወያኔ እስር ቤቶች ውስጥ ኢስብአዊ የወሲብ ጥቃት ይቁም!!!

የወያኔ እስር ቤቶች በዓለም ዓቀፍ ስብአዊ መብት ኮሚሽን ይጎብኙ!!!

ኢት-ኢኮኖሚ /ET- ECONOMY

‹‹የህወሓት መንግሥት ሲያረጅ፣ የአዋጅ ፋብሪካ ይሆናል!!!››

‹‹ከኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማህበር ዶክተር እሸቱ ጮሌ ክበብ›› ክፍል ሁለት

ህወሓት የጦር አበጋዞች መንግሥት TPLF WARLORDS STATE የወያኔ ፋሽስታዊ ‹የአስቸኮይ ጊዜ አዋጅ!› ይነሳ!!! ያለ ኢኮኖሚ ነፃነት የፖለቲካ ነፃነት የለም!!!

ለኢትዮጵያ ሃገራዊ ንቅናቄ፣

ለኢትዮጵያዊያን የጋራ ግበረ ኃይል፣

ለኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ፣

ለኢትዮጵያውያን ተጋሩ፣

ለሁሉም ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶችና የሲቪክ ማህበራቶች፡-

‹‹የወያኔ የዘር-ግምብ በኢትዩጵያ ይፈርሳል!!!››

በእምዬ ኢትዩጵያ ግዛት በየብስ፣በምድር ባቡር ሃዲድና በመኪና መንገድ፣በዓየር በአውሮፕላን፣ የወያኔ የኢኮኖሚ ኢምፓየር በኢትዩጵያ ምድር እንደ ሸረሪት ድር፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምዕራብ እስከ ምስራቅ፣ በመላ ሀገሪቱ ተዘርግቶ የግብርና፣ኢንዱስትሪና የአገልግሎት ዘርፎቹን ላለፈው 27 ዓመታት በመቆጣጠር ህዝቡን በድህነት አረንቆ ከቶል፣ ምጣኔ ኃብቱ ተሸመድምዶል፣ የወጣቶች ሥራ አጥነት አገሩን አጥለቅልቆል፣  ከአጥናፍ አጥናፍ የወያኔ የሙስና መረቡን ዘርግቶ እንደ መጅገር ተጣብቆ የደሃውን ህዝብ ደም በመምጠጥ ላይ ይገኛል፡፡ የህወኃት የጦር አበጋዞች መንግሥት እናት ሃገራችንን ለቻይና ስውር ቅኝ አገዛዝ አሳልፈው ሰጥተዋል፡፡ በሃገሪቱ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ሁኔታ፣በሃገሪቱ ያሉ የኢኮኖሚ ዘርፈ ብዙ የማህበራዊ ችግሮች መካከል፣

1-በኢትዩጵያ በ2008ዓ/ም 10.2 ሚሊዩን ህዝብ፣በ2009ዓ/ም 5.6 እስከ 7.8 ሚሊዩን ህዝብ፣ ድርቅና ያስከተለው ርሃብ መጠነ ሰፊ መሆኑ ተገልፆል፡፡ የዕርዳታ ድርጅቶች ምላሽ በጣም ተቀዛቀዘ መሆኑ ታውቆል፡፡ ህዝቡን መመገብ ያልቻለ የህወሓት የጦር አበጋዞች መንግሥት መወገድ አለበት፡፡

2-በኢትዩጵያ በገጠር 14 ሚሊዩን በከተማ በ2008ዓ/ም የጀመረው 4.7 ሚሊዩን ለሚሆኑ ሰዎች የምግብ ዋስትና ፕሮግራም (በሱፍቲ ኔት ፕሮግራም)  ተጠቃሚ ናቸው፡፡ በአዲስ አበባ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው 400 ሽህ ሰዎች በምግብ ዋስትና ታቅፈዋል፡፡በምግብ ዋስትና ፕሮግራም ጥናት መሠረት 25.7 በመቶ የሚሆኑ የከተማ ነዋሪዎች ለምግብ ዕጦት ተጋላጭ እንደሆኑ ይገልፃል፡፡ ህብረተሰቡ በእቃዎች የዋጋ ግሽበት፣ በቤት ኪራይ ክፍያ ይሰቃያል፡፡

3-በ1994 የህዝብ ቆጠራ በኢትዩጵያ 988,853 የአካል  ጉዳተኞች መኖራቸው ታውቆል፡፡ ከኢትዩጵያ 53,073,322 ሚሊዩን ህዝብ ብዛት 1.9 በመቶ ዜጎች የአካል ጉዳተኞች ነበሩ፡፡ በ2008 ዓ/ም ምን ያህል የአካል  ጉዳተኞች ይኖራሉ፣

4-በኢትዩጵያ ውስጥ 4.6 ሚሊዩን ህፃናቶች ከወላጆቻቸው አንዱን በሞት የተነጠቁ ናቸው፡፡ በዚህም የተነሳ ሃገሪቱ ከዓለማችን የሙት ልጆች መኖሪያ ለመሆን በቅታለች፡፡ወያኔ 25 ሽህ ህፃናቶችን በማደጎነት የሸጠ መንግስት ነው፡፡

5-በኢትዩጵያ ውስጥ 1.2 ሚሊዩን ህዝብ በኤችአይ ቪ/ኤድስ በሽታ ጋር አብሮ ይኖራል፡፡ 800 ሽህ ህጻናት ከዚህ በሽታ ጋር በተያያዘ ወላጃቸውን አጥተዋል፡፡ በአዲስ አበባ መቶ ሃያ ዘጠኝ ሽህ ሴተኛ አዳሪዎች በዝሙት ሥራ እንደሚተዳደሩ በጥናት ተረጋግጦል፡፡

6-በኢትዩጵያ በዓመት ከአንድ ሽህ ዜጎች መካከል ዘጠኙ ወደ ሌሎች አገራት ይሰደዳሉ፡፡ በ2015 እኤአ በኢትዩጵያ የሥነ-ህዝብ ቁጥር 99,465,819 ሚሊዩን ውስጥ 895,192 ሽህ ህዝብ በዓመት ከሃገሩ ወጥቶ እንደሚሰደዱ ተገልፆል፡፡ ብዙ ወጣቶች በሳህራ በረሃ እያቆረጡና ከውቅያኖስ እየሠመጡ፣ በአይሲስ እየተሠየፉ ሞተዋል፡፡

7-በኢትዩጵያ የነፍስ ወከፍ አመታዊ ገቢ ከ400 ዶለር እንደሆነና 39 በመቶ ሚሆነው ህብረተሰብ ክፍል 1.25 ዶለር በቀን ገቢ ያለውና ዕቃና ሸቀጣ ሸቀጥ የመግዛት አቅሙ ከድህነት ወለል በታች መሆኑ በጥናት ተረጋግቶል፡፡ በኢትዩጵያ ስብዓዊ ልማት ኢንዴክስ 0.363 ሲሆን በአለማችን ከሚገኙ 187 አገራቶች 174ኛ ደሃ ሃገርነት ተፈርጃ ትገኛለች፡፡ ኢህአዴግ በውሽት ኢኮኖሚያችን በሁለት አሃዝ በተከታይ ዓመታት አደገ የሚለው ውጤቱ በዚህ ጥናት ውድቅ ሆኖል፡፡

 

በሃገራችን የኢኮኖሚ ነፃነት ከሚገለፅባቸው ዋና ዋና መርሆዎች ውስጥ አንዱንም አታሞላ፡፡ አንደኛው የህግ የበላይነት፣የፍትህ ሥርዓት መከበር፣የንብረት ባለቤትነት መብት መከበር፣ የመንግሥት ሙስናን ለመዋጋት ያለው አቅም የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ፡፡ የሃገር ውስጥና የባህር ማዶ ኢንቨስተሮች የህግ ሉዓላዊነት ያለበት ሃገር መዋለ-ንዋያቸውን አፍሰው በነፃነት ኃብት ማፍራት ይሻሉ፡፡ ህግና ፍትህ ባለበት ሃገር ቀጥተኛ የውጪ ኢንቨስትመንት ፍስት ከአመት አመት እንዲጨምር ያደርጋል፡፡ በኢትዩጵያ ህግ የለም፣ ፍትህና ርትህ አይሠራም፣ የዜጎች ንብረት የማፍራት መብት የለም፡፡ በኢትዩጵያ የህወሓት መንግሥት በሞኖፖል የተያዙ ንብረቶችና ኃብቶች መካከል፡-በሃገሪቱ የመሬት ኃብት የህወሓት መንግሥት በመሆኑ የግብርና፣የማኑፋክቸሪንግና አገልግሎት ዘርፍ ክፍለ ኢኮኖሚ እድገቱ የቀጨጨ ለመሆን በቅቶል፡፡ ህዝባችን የመሬት ኃብት ንብረት የመያዝ መብትና ነፃነት ስለሌለው በርሃብ አለንጋ ይሰቃያል፡፡ ህዝቡን መመገብ የማይችል መንግሥት ህዝቡን መግዛት አይችልም፡፡

 

ሁለተኛው መሠረታዊ የኢኮኖሚ ነፃነት መመዘኛ የመንግሥትን የፊስካልና የወጪ አቅም የሚመለከት ነው፡፡ መንግሥት ምን ያህል ታክስ ይሰበስባል; ምን ያህል ወጪ ያደርጋል; የሚሉት መመዘኛዎች በዚህ መሰረት የሚቃኙ ናቸው፣የታክስ ገቢው ከአጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት ያለው ድርሻ 17 በመቶ ለማሳደግ ከፍተኛ የታክስ አስተዳደር ጥረት ለማድረግ ቢታሰብም በኦሮሚያና አማራ ክልሎች በተነሳ ህዝባዊ አመፅ ግብር የመሰብሰብ ችግር ገጥሞታል፡፡ የፊስካል ፖሊሲና የመንግስት ፋይናንስ አፈፃፀም፣‹‹ጠቅላላ የታክስ ገቢ በ2002 ከነበረበት 43 ቢሊዩን ብር በ2006 መጨረሻ ወደ 133 ቢሊዩን ብር ሲሆን፣  የተሰበሰበው ገቢ በራሳ አቅም ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶችን ለማካሄድ አስችሎ ነበር፡፡ በ2007 በጀት ዓመት የታክስ ገቢ ከጠቅላላ የሃገር ውስጥ ምርት ያለውን ድርሻ ወደ 15 በመቶ ለማድረስ የታቀደ ቢሆንም በ2006 የበጀት ዓመት የተሰበሰበው የታክስ ገቢ ከጠቅላላ የሃገር ውስጥ ምርት ያለው ድርሻ 12.7 በመቶ ብቻ ነው፡፡ በ2010ዓ/ም 199 ቢሊዩን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ 90 ቢሊዩን ብር ብቻ በመሰብሰብ የታክስ ገቢው ዝቅ ብሎል፡፡ከሳህራ በታች ያሉ የአፍሪካ ሃገራት አማካይ አፈፃፀም 15 በመቶ ነው፡፡ ከመንግስት ጠቅላላ የወጪ በጀት ውስጥ ወደ 60 በመቶው የሚጠጋው ለካፒታል ኢንቨስትመንት ሲደለደል፣ ቀሪው 40 በመቶ ገደማ ብቻ የመደበኛ ወጪ ለመሸፈን ሲመደብ ቆይቶል፡፡ በዕቅድ ዘመኑ የተሰበሰበው የመንግስት ገቢ በመደልደል የበጀት ጉድለቱ ከ3 በመቶ እንዳይበልጥ በማድረግ ጥብቅ የፊስካል ፖሊሲ ተግባራዊ ለማድረግ በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን  እቅድ ታቅዶ  ነበር፡፡ በ2008፣በ2009ና 2010ዓ/ም በኦሮሚያ ህዝባዊ እንቢተኛነትና በአማራ ህዝባዊ ተጋድሎ የግብርና የታክስ መሰብሰብ ዕቅድ ‹ላም አለኝ በሰማይ ፣ወተቶንም አላይ› ሆነ፡፡ ከህዝብ ታክስ መሰብሰብ ያልቻለ መንግሥት በህዝብ የተጠላ መንግሥት ነው፡፡ የስልጣን እድሜውም አጭር ነው፡፡ ህወሓት ከህዝብ ግብር መሰብሰብ ካልቻለ ለመከላከያ ሠራዊቱ፣ለፖሊስ፣ለደህንነቱ፣ለፊዴራልና ለክልሎች ለሲቪል ሠራተኞችና አስተዳደር የሚከፈል ደሞዝ ስለማይኖር ከሥልጣን መንበሩ ይወገዳል፡፡ ወያኔ የአስቸኮይ ግዜ አዋጁ ዳግም በማወጅ በጉልበት ግብር ሊሰበስብ ይፈልጋል፣ የህዝብ ልጆች እየገደለ መግዛት ይፈልጋል፣ በሙስናና በኮንትሮባንድ ንግድ የከበሩ አይነኬ የጦር መኮንኖች በመላ ሃገሪቱ ህገወጥ የድንበር ዘለል ንግድ በመዘርጋት የሃገሪቱን ኢኮኖሚ አውድመዋል፡፡

 

ሦስተኛው የኢኮኖሚ ነፃነት መመዘኛ ኢኮኖሚው እንዴት እንደሚተዳደር የሚያሳይ ሲሆን፣በኢትዩጵያ መንግሥት ‹‹ልማታዊ መንግሥት›› ስም  መንግሥታዊው ዘርፍ የግሉን ዘርፍ ኃብትና ሊሠራ የሚችለውን ኢንቨስትመንት ሥራ ሁሉ በመሻማት የግሉን ዘርፍ እድገትና ሚና አጨናግፎታል፡፡ የኢትዩጵያ መንግሥት ‹‹ልማታዊ መንግሥት›› ነው ወይስ ‹‹የህወሓት የጦር አበጋዞች መንግስት›› ነው የሚለውን የኢትዩጵያ  የፖለቲካ ኃይሎች አቆም መውስድ ይገባቸዋል፡፡ አሊያም በኢትዩጵያ ያለው መንግስት ምን ዓይነት መንግስት ነው የሚለው በጥናት ተደግፎ መቅረብ አለበት፡፡ በሃገሪቱ ዴሞክራሲያዊ አስተዳደር ለመመስረት የብዙሃን ፓርቲዎች የውድድር ሥርአት ሠፍሮ፣በህዝብ ድምፅ አሸናፊው ሥልጣን የሚይዝበት የምርጫ ስርዓተ-አሥተዳደር መገንባት አለበት፡፡

የወያኔ ኢፈርት ኢንተርፕራይዞች፡- በወያኔ ባለሥልጣኖች የሚተዳደሩ የሜቴክ ድርጅቶች የሙስና መፈልፈያዎች፣ የእውቀትና የብቃት ችግር የተንሠራፋባቸው፣ በሥልጣን በመጠቀም የግል ፍላጎት ተጠቃሚነትን የሚያስፋፉ፣እንዲሁም ከለላን የሚያበረታቱ፣ የፖለቲካና የዝምድና አሰራር የነገሰበቸው ናቸው፡፡ የወያኔ ኢፈርትና ሜቴክ ድርጅቶች ንግድን ከመፍጠር ይልቅ የግል ዘርፉን ንግድ ፍሰቱን የሚቀለብሱ ተቆማት ናቸው፡፡ በዚህም የንግድ መዛባትን በመፍጠር፣ውድድርን በማክሰም፣በመንግሥት እጅና ጥበቃ ከውድድር ውጭ ሆነው የሚተዳደሩ ድርጅቶች ናቸው፡፡ እነዚህ የወያኔ ድርጅቶች በነፃው ንግድ ተወዳዳሪ ሳይሆኑ ባንኮችን እየመዘበሩ ሃገራችንን ለውድቀት የዳረጉ የፖለቲካ ንግድ ድርጅቶች ናቸው፡፡ የግሉ ዘርፍ የንግድ ተቆማት በሚደረግበት አድሎ ከጫዋታው ውጪ ለመሆን ችሎል፣ በዚህም ለህብረተሰቡ በእቃዎች የዋጋ ግሽበትና እጥረት ይሰቃያል፡፡

 

አራተኛ ኢኮኖሚው ለዓለም ገበያ ክፍት መሆን፣የንግድ፣የኢንቨስትመንት፣እንዲሁም ባንኮችና መድህን ድርጅቶች በተመለከተ፤በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን  እቅድ ዘመን ጠቅላላ የመንግሥትና የግል ኢንቨስትመንት ከጠቅላላ የሃገር ውስጥ ምርት የሚኖረው ድርሻ 41.3 በመቶ እንዲሆን ተገምቶ ነበር፡፡ ከጠቅላላ ኢንቨስትመንቱ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛውን በአገር ውስጥ ቁጠባ ለመሸፈን እንዲቻል በዕቅድ ዘመኑ የአገር ውስጥ ቁጠባ ምጣኔን ወደ 29.6 በመቶ ለማድረስ ግብ ተጥሎ ነበር፡፡ ሆኖም በኦሮሚያና አማራ ክልሎች በተነሳ ህዝባዊ አመፅ የሃገር ውስጥ የባህር ማዶ ኢንቨስተሮች ንብረት የሆኑ ፋብሪካዎችና እርሻዎች መውደም ምክንያት የታቀደው አልተሞላም፡፡ በመቀጠልም ከ2008 እስከ 2009/2010ዓ/ም የውጭ ንግድ ገቢ አሽቆለቆለ፣ በአንጻሩ የገቢ ንግድ ወጪ በማደጉ የንግድ ሚዛኑ ተናጋ፡፡ በዚህም የተነሳ ያልተረጋጋ የብር ምንዛሪ ተመንና የውጭ ምንዛሪ ክምችት እጥረት፣የመንግሥትና የልማት ድርጅቶች በዕዳ ክፍያ ጫና ተሰነጉ፡፡ በአጠቃላይ  የአገሪቱ የፋይናንስና የባንክ ኢንዱስትሪው ልማቱ የሚጠይቀውን ፋይናንስ የማቅረብ ብቃት ወደቀ፡፡ በሃገሪቱ የፋይናሻል ዘርፍ ውድቀትና ኪሣራ ደርሶባቸዋል፡፡ የመንግሥታዊው ንግድ ባንክ፣ የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ፣የኢትዩጵያ ልማት ባንክ ከባድ ኪሣራ ደርሶባቸዋል፡፡ ብሄራዊ ባንክ ገንዘብ ከምድረ ሱዳን ብር እንደ ወረቀት በማተም፣የዋጋ ግሽበቱንና የኑሮ ውድነቱን አባብሶታል፣ የውጪ ንግድ ገቢ በድርቅ ተመቶል፣ የውጭ ምንዛሪ እጥረት በጣም ተባብሶል፣በእጥረቱ ምክንያት የኮንስትራክሽን ስራዎች በአብዛኛው ተቆርጠዋል፣ ሜጋ ፕሮጀክቶች ቆመዋል፣በሃገሪቱ በታወጀው ‹አስቸኮይ ጊዜ አዋጅ› የተነሳ በባህር ማዶ ኢንቨስተሮች ሽሽት የተነሳ፣ ይደረግ የነበረው ቀጥተኛ የውጭ ኢንቨስትመንት ፍሰት አሽቆልቁሎል፣ የሆቴልና ቱሪዝም ገቢም ነጥፎል፡፡ ወያኔ ዳግም ‹አስቸኮይ ጊዜ አዋጅ› አውጆል፡፡

በ2008ና በ2009 ዓ/ም በኦሮሚያ ህዝባዊ እንቢተኛነትና በአማራ ህዝባዊ ተጋድሎ የተነሳ የህወሓት የጦር አበጋዞች መንግስት በኢትዩጵያ ብሄራዊ ባንክ ዘርፎ ያከማቸውን 850 ኪሎ ግራም ወርቅ ወደ መቐለ ማጎጎዙን ውስጥ አዋቂዎች ገልጸዋል፡፡ ህወሓት በዘረፋ ያገኘው 850 ኪሎ ግራም ወርቅ 850,000 ግራም ወርቅ ይሆናል ይሄን ለ29 ግራም (1 ወቄት ማለት ነው) ስናካፍለው 29,310 ወቄት ወርቅ ይሆናል ይሄን በ1 ወቄት ዋጋ 1,218.80 ዶላር ስናባዛ 35,773,448 ሚሊዩን ዶላር ይሆናል በብር ስንቀይረው ደሞ በ20.34 ሲባዛ 726,768,548.7ሚሊዩን ብር የህወሃት ጦር አበጋዞች በብሄራዊ ባንክ አከማችተዋል ማለት ነው፡፡ ዝርዝሩን ከድረ-ገፁ ያንብቡ፡፡

 

‹‹Since 1999, geological map survey has been conducted so as to identify the type, coverage and amount of mineral resources in our region. Up to now, the activities of collecting geological information from 24,780 meter square and consolidating reports have been finalized. The geological map coverage of our region has reached 46.2% and around 850 kg gold is already deposited in the national bank of Ethiopia. In this regard, there were some limitations which need due attention such as fulfilling enough skilled manpower and inspecting equipments and laboratory services among others.›› (Tigray Regional State, Five Years 2010/11-2014/15, Growth & Transformation Plan, Bureau of Plan and Finance, September 2003 E.C, Mekelle, page 17) Next Five Years (2010/11-2014/15) Regional GTP: Tigray Region Plan and Finance Bureau.

 

የባንኩ ኢንዱስትሪ፡-በሃገሪቱ የሚንቀሳቀሱት የመንግሥትና የግል  የአገር ውስጥ ባንኮችና መድህን ድርጅቶች ብቻ ናቸው፡፡ የነዚህ ባንኮች ደንበኞች በአብዛኛው የአገር ውስጥ ባለኃብቶች ናቸው፡፡ የሃገር ውስጥ ባንኮች የሚንቀሳቀሱበት መስኮች ከውጭዎቹ የተለዩ ናቸው፡፡ የውጭ ባንኮች ወደ ሃገር ውስጥ ቢገቡ ለትልልቅ ሜጋ ፕሮጀክቶችና ለዓለም አቀፍ ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶች ፋይናንስ በማቅረብ ያለውን የፋይናንስ ችግር የውጪ ምንዛሪ ጠኔ ይቀርፋሉ፡፡ በኢትዩጵያ፣ የሃገር ውስጥ ባንኮች ውስጥ 1 ቢሊዩን ዶላር ማበደር የሚችል ባንክ የለም፡፡  ለሃገር ውስጥና ለውጪ ባለኃብቶች የካፒታል አቅርቦት ችግር ሲገጥማቸው የውጭ ባንኮች በሃገሪቱ ውስጥ እንዳይሰሩ በመታገዳቸው የካፒታል አቅርቦት፣ የውጪ ምንዛሪ ችግር፣ የከፋ ማነቆ ሆኖል፡፡ በዚህም የተነሳ የኢንቨስትመንትና የፋይናንስ ነፃነት በተመለከተ ሔሪቴጅ ፋውንዴሽን ጥናት መሠረት በተጠቀሱት ሁለት መስኮች አገሪቱ በእየአንዳንዳቸው ከ100 ያስመዘገበቻቸው 20 ነጥብ ብቻ ነው፡፡ የሔሪቴጅ ፋውንዴሽን ሪፖርት፣ኢትዩጵያን በአብዛኛው የኢኮኖሚ ነፃነት ከሌላቸው አገሮች ተርታ አስቀምጦታል፡፡ከ100 ነጥብ 51.5 በመቶ ያገኘችው ኢትዩጵያ፣ በመንግሥት ጫናና ቁጥጥር ሥር የሚገኙ ተቀማት ያስከተሉትን ተፅዕኖ፣መንግሥት ወሳኝ የሚላቸው የኢኮኖሚ አውታሮች ለውጭ ኢንቨስተሮች ክፍት አለመደረጋቸውና ሌሎችም ተመዝነው አገሪቱ ነፃነት የሌላት እንድትባል ማድረጉን ሮበርትስ ይተነትናሉ፡፡

ዴሞክራሲያዊ መብቶች በታገዱበት ሃገር፣የወያኔ የመጨረሻው አዋጅ ዳግም በወርሃ የካቲት 9 ቀን 2010ዓ/ም  ‹የአስቸኮይ ጊዜ አዋጅ› በታወጀባት ሃገር ከባህር ማዶ ኢንቨስተሮችና ቱሪስቶች የሚገኘው ገቢ ይቆረጣል፡፡ የወያኔ ፋሽስታዊ አገዛዝ ድቅድቁ ጨለማ በብርሃን ይተካል፣ አንድ ቀን ባርነት በነፃነት ይተካል፣ አንድ ቀን ለቅሶችን በሣቅ ይቀልጣል፣ ጥላቻ በፍቅር፣ ድንቁርና በዕውቀት ይተካል፣የተደራጀ፣የነቃና የታጠቀ ህዝብ ያቸንፋል! ያሸንፋል! የህወሓት አረመኔዊና ሰይጣናዊ ሥራ በማጋለጥ ወጣቶች በፅናት እንዲታገሉና ሥርዓቱን እንዲያንኮታኩቱ ብርታት፣ ጥንካሬና ፅናት በሁሉም ዜጎች ህሊና ተቀርፆል፡፡ በወያኔ እጅ ሳይወድቁ፣ በፋኖነት  ነፃ ግዛት መስርተው፣ ለሃገር ለወገን መታገል፣ የወያኔን አንባገነን ሥርዓት መንግሎ ለመጣል ግዜው አሁን ነው፡፡ የነፃነት ደውል ተደውሎል፡፡ በእናት ሃገራችን ሁለተኛና ሦስተኛ ዜጋ ሆኖ መኖር እስከመቼ!!! ሃገራችን የህዝቦች እስር ቤት ሆና ለልጅ ልጆቻችን ባርነትን ከማውረስ ሞትን ተሠልፎ የሚጠብቁ እልፍ አእላፍ ዜጎች ያሎት ሃገር ናት!!! የህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት ዘመን ህዝቡ የዕለት ዕለት ኑሮውን በፍርሃት ነው የሚኖረው፣ ነገ ከሥራ ቢያባርሩኝ፣ ነገ ከመኖሪያዬ ቢያፈናቅሉኝ፣ በየመንገዱ ወታደር ቆሞ ኪስህን ይፈትሽሃል፣ ነገ ምን አርጉ ይሉን ይሆን በሚል የደህንነት ስጋት ውስጥ ነው የሚኖረው፡፡ በሌላ በኩል የሸቀጣ ሸቀጦች የዋጋ ግሽበት፣ የቤት ኪራይ በየግዜው መጨመር፣ የልጆች  ትምህርት ቤት ክፍያ መጨመር፣ ለግድብ አዋጡ፣ ቦንድ ግዙ፣መልዕክቱ ሁሉ ገንዘብ አምጡ ነው፡፡ ዜጎች አንድ ነገር ለማስፈፀም ያለ ጉቦ የምትፈፀም አንዳችም ነገር የለ፣ ከቀበሌ አስተዳደር፣እስከ መንግሥት መስሪያ ቤቶች፣ ባንኮች ብድር ለማስፈቀድ፣ፖሊስ ጣቢያ ፖሊሶች፣ ፍርድ ቤት ዳኞች ወዘተ ሁሉ ቦታ ጉቦኛው መአት ሆኖል፡፡ በአጠቃላይ ሥርዓቱ ገምቶል፡፡

የህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት አድሎና በደል በፖለቲካ ተሳትፎ በእነሱ ፖለቲካ ያልታቀፉ ዜጎች ሁለተኛ አሊያም ሶስተኛ ደረጃ ዜጎች ናቸው፡፡ ትምህርት ለመማር፣ ስራ ለመያዝ፣ ማዳበሪያ ለመግዛት፣ከማይክሮ ፋይናስ ድርጅቶች ገንዘብ ለመበደር ወዘተ በድርጅቶቹ በወጣቶች ፣በሴቶች፣ በሠራተኞች ማህበር፣በመምህራን፣በዩኒቨርሲቲ አስተማሪዎች፣ በገበሬ ማህበራት፣ በሸማቶች ማህበራት ወዘተ አንድ ለአምስት መደራጀትና ለህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት  መሰለል ዋነኛ ሥራቸው ነው፡፡ በዚህ መልክ ያደራጆቸው ጥቂት ሚሊዩን ዜጎች ቢገመቱ ለእነሱም ከተስፋ እንጀራ በስተቀር ለብዙሃኑ የደረሰ ኩርማን እንጀራ የለም፣ እንዲውም ለድርጅቶቹ ወርሃዊ መዎጮ፣ ልማት መዋጮና ስብሰባ ስለሰለቻቸው አንዳንዶቹ ከአባልነት እንደወጡ ይታወቃል፡፡ የህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት ህዝቡን በኮንዶሚኒም ቤቶች ታገኛለህ በሚል ይደልላል፣ በደሞዝ ጭማሪ ይደልላል፣በአነስተኛና ጠቃቅን ስራ እድል ይደልላል ሆኖም ከዚህ ተጠቃሚው ትንሽ ሰዎች ናቸው፡፡ የመጨረሻው የወያኔ ፊሽካ ‹የአስቸኮይ ጊዜ አዋጅ!› በራሱ ጊዜ ይከሽፋል ወያኔ አዋጁን ተግባራዊ ማድረግ አይችልም፡፡ የመከላከያ ሠራዊቱ፣ሚሊሻው፣ልዩ ፖሊሱ ኃይል ህዝባዊውን ትግል መቀላቀሉ አይቀሬ ነው!!! የግዜ ጉዳይ ነው!!! ከመላከያ ሠራዊቱ የህዝብ አካል ነው፡፡

 

በሃገሪቱ ከ65 በመቶ ህዝብ በወጣትነት የዕድሜ ክልል የሚገኙ በመሆኑ ወጣት ተኮር ኢኮኖሚ የሥራ ፈጠራ ላይ ያተኮሩ የኢኮኖሚ ፖሊሲና ስትራቴጅ ያልነደፈ በሙስና የተዘፈቀ መንግስት የወጣቶችን ጥያቄ ሊመልስ አይችልም፡፡ በኢትዩጵያ በሚገኙ 33 ዩኒቨርሲቲዎች፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቆም በየዓመቱ ከ100,000 ሽህ በላይ ተመራቂዎች ይወጣሉ፡፡ የወያኔ/ኢህአዴግ መንግሥት በነደፈው የትምህርት ፖሊሲ በከፍተኛ ትምህርት ተቆም ለመማርና የሥራ እድል ለማግኘት በእነሱ የፖለቲካ ድርጅቶች መታቀፍ አንዱ መመዘኛ ከሆነ አመታት በመቆጠሩና ወጣቶቹ ተመልምለውም የሥራ እድል ባለመኖሩ ወጣቶች በስርዓቱ ተስፋ ቆርጠዋል፡፡ ህወኃት/ኢህአዴግ መንግስት ከሃያ ሽህ በላይ የፖለቲካ ካድሬዎቹን በተለያዩ የቻይና ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በማስተማር የአፋኝ ሥርዓቱን በአዲስ ቴክኖሎጅና ቢሮክራሲውንና የስለላ መረቡን በሃገሪቱ ውስጥ ለመዘርጋት ከቻይና መንግስት ድጋፍ ተደርጎለታል፡፡

 

የሃገሪቱን አጠቃላይ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ጉዳዩች ሁለንተናዊ ገፅታዎች፣ የቻይና መንግሥት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ በአፍሪካ  የቅርብና የረዥም ጊዜ ዕቅድ የተመሠረተው፣ በጥሬ ኃብት ዘረፋ፣የመዕድን ኃብት (አልማዝ ፣ወርቅ፣ብረት፣ ነዳጅ፣ የመሬት ቅርምት ወዘተ ኃብት ብዝበዛ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡  በአፍሪካና ኢትዩጵያ የቻይና ስውር ቅኝ አገዛዝ እንደ ቻይና ግምብ ክፍለአህጉሩንና የሃገራቱን ፖለቲካ ምህዳር በአንድ አውራ ፓርቲ መሪነት ተቆጣጥረው የአፍሪካ መሪዎችንና የወያኔን እጅ ጠምዝዘው፣ሁሉን ማስፈፀም በመቻላቸው፣ በኢኮኖሚው፣ በኢንዱስትሪ፣ በአገልግሎትና  በግብርናው ዘርፎችን በመሬት ቅርምት ኃብት መቆጣጠር ችለዋል፡፡ የቻይና መንግሥት ለአፍሪካ አንባገነን ገዥዎች ከስልጣን መንበራቸው እንዳይወድቁ ድጋፋቸውን በመስጠት በቴሌኮምኒኬሽን ዘርፍ የስለላ መረባቸውን በመዘርጋት በማህበራዊ ድረ-ገፆችን፣ሞባይሎችን፣ኢንተር ኔት ወዘተን በመዝጋት የህዝብን ድምፅ በማፈንና፣የህወሓት የጦር አበጋዞች መንግስት በህዝባዊ ትግል እንዳይወድቅ ድጋፍ በመስጠት ጥቅማቸውን ያስጠብቃሉ፡፡ የሃገራችን ጉዳይ ያገባናል የምንል ኢትዩጵያውያን ትግላችንና አጀንዳችን የመሬት ኃብት ጥያቄ የህልውና ብቸኛ ጉዳይ ነው፡፡ ህወኃት በሃገራችን የተከናወነው የመሬት ቅርምት ለህዝባችን የመኖርና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ ነው፡፡ ከመሬታችን ከምድራችን የመነቀልና ያለመነቀል ጥያቄ ነው ህወኃት በጋምቤላ፣ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በአፋር፣ በቤኒ-ሳንጉል ጉሙዝ፣ በደቡብ ክልሎች የህዝብ መሬትን ቸርችሮ ለባህር ማዶ ዜጎችና ለህወኃት የፖለቲካ ድርጅቶች አካፋፍሎል ድግምም መሬት ለመቸብቸብ በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ህወኃት በገጠርና በከተማ በተለይ በአዲስአበባ፣በአዳማ፣በደብረብርሃን፣በጎንደር፣በባህርዳር፣በመቀሌ፣ወዘተ የከተማ መሬት ቅርምት ወያኔ በኢኮኖሚ በልፅጎ ለዘመናን የኢትዩጵያን ህዝብ በፖለቲካ ለመግዛት እንደሆነ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡

 

ለዚህም የወያኔ ሴራ የቻይና መንግሥት አባሪና ተባባሪ እንዲሁም ከመሬት ቅርምቱ ዘረፋ ዋነኛ ተጠቃሚ በመሆን በጋራ በመግዛት ላይ ይገኛሉ፡፡ ትግላችን መራራ ነው፣ የምንታገለው የተነጠቅንውን መሬት ለማስመለስ ነው፣ ‹‹መሬት የመንግሥት ኃብት ነው›› የሚለውን የደርግና የወያኔ መንግሥትን አዋጅ ለመሻር ነው፡፡ የምንታገለው   ለራሳችን ለልጆቻችን ለቀጣዩ ትውልድ በነፃነት፣ በእኩልነትና በሰላም በእውነተኛ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲ ሥርዓት ዘርግተን መሬታችንን አስመልሰን በጋራ አብሮ ለመኖር ህልውናችን ስንል ብቻ ነው፡፡ የህወኃት/ኢህአዴግ መንግስትንና የቻይናን ስውር ቅኝ አገዛዝ በህዝባዊ ትግል ማስወገድ የወቅቱ ብቸኛ አጀንዳችን ነው፡፡ ‹‹ዝንጀሮ መጀመሪያ መቀመጫዬን አለች!›› እንደሚባለው የአበው ብሂል ትግላችን የገጠርና የከተማ በመሬት ዘረፋ ለማስመለስ ነው፡፡ ወያኔ ከእርስታችን ነቅሎናል! ወያኔ ከመኖሪያችን ነቅሎናል! በሪል ስቴት ልማት ስም!፣በኮንዶሚኒየም ግንባታ ስም!፣ በልማት ተነሽዋች ስም የመንደሮች ነዋሪዎች ተነቅለዋል፣የወያኔ ኢፈርት በእኛ መሬት ላይ ተተክሎል፣ሜቴክ መሬቱን ወስዶል፣ ሜድሮክ መሬቱን ዘርፎል፣ መከላከያ መሬቱን ተመርቶል፡፡ ህዝቡ ተፈናቃይ፣ ወያኔ አፈናቃይ!፣ ህዝቡ ለስደት፣ ወያኔ ለመስፋፋት፣ይሄን ስልጣን ለወያኔ ማንም አልሰጠውም!!!  ቻይና፣ ህንድ፣ ፓኪስታን ወዘተ በእርሻ ልማት ስም!፣በአበባ ልማት ስም! በኢንዱስትሪያል ዞን ስም!፣ በመለስ ፋውንዴሽን ስም!፣ መሬቱን ተቀራምተዋል፤ለዚህ ነው እኛን የሚያስተባብረን የመሬታችን ጉዳይ ብቻ የሚሆነው!!! ሁሉም ኢትዩጵያዊ ዜጋ በያለበት እየተደራጀ እየታጠቀ መሬቱን የማስመለስ ትግል ያድርግ፣ ሁሉም ከመሬቱ ተጠቃሚ የነበረ መሬቱን ለማስመለስ ቆርጦ ከተነሳ የወያኔና የቻይና የአገዛዝ እድሜ ያጥራል፡፡

 

የሃገራችን መሬት ያፈራው ቡና፣ሰሊጥ፣ቦለቄ፣ጫት ወዘተ ወደ ውጪ ልከው ባገኙት የውጪ ምንዛሪ የጦር መሳሪያ ገዝተው እኛኑ ይገሉናል፣ ያስሩናል፣ ያሰድዱናል፡፡ የሃገራችን መሬት የተዛቀውን ከለገደንቢ፣ አዶላ፣ መተከል፣ትግራይ የወርቅ መዕድን ሸጠው መገደያችንንና እስርቤታችንን  እናመቻቻለን!!! ፍርሃታችን ቅጥ አቶል፣ሃፍረታችን አይን አውጥቶል፣ማናሳድገውን ልጅ እየወለድን ስናስገድል የደርግና ወያኔን ሁለት መንግስት አስተናግደናል፣ ሊበቃ ይገባል ከባርነት ህይወትን ከመግፋት ተከብሮ መሞትን እንምረጥ፡፡ ያለ መሰዋትነት፣ ያለትግል ወያኔ አይወድቅም! በትግሉ ለሚሳተፉ ጀግና አርበኞቻችን ከድል በኃላ የመሬት፣የቤት፣የሥራ፣የህክምና ወዘተ ጥቅማ ጥቅሞች ሃገሪቱ አቅም በፈቀደ መልክ ይበረከትላቸዎል፡፡ ክብር መስዋትነት ለከፈሉ የህዝብ ልጆች  ለሆኑ አርበኞች ቤተሰቦች አስፈላጊው ገፀ-በረከት ይደረግላቸዋል፡፡ የታገለና ያልታገለ፣ አርበኛና ባንዶዎች፣በእኩል ሚዛን አይመዘኑምና፡፡ በዚህ አጋጣሚ ቃለ-መኃላ የፈፀመ የኢትዩጵያ መከላከያ ሠራዊት ለዚህ ግዳጅ የስራው ብሃሪ እንዲሳተፍ ህዝባዊውን ትግሉ እንዲቀላቀሉና እንዲመሩ፣ በህዝብ ስም ጥሪ ቀርቦላቸዋል፡፡ ሃገሪቱን ለወያኔ ጦር አስረክበው የኮበለሉ የሃገሪቱ ሠራዊት በዚህ ሃገራዊ ጥሪ አገራቸውንና ህዝባቸውን ሊክሱ ይገባል፡፡ የምታገለው በመጀመሪያ ለእራሴ ነፃነት ነው፣የተዘረፍኩትን ለማስመለስ ነው፣ ያጣሁትን ፍትህና ርትህ ለማስመለስ ነው፣በሃገሬ ተከብሬ እንደሰው ለመኖር ነው፣ ስለዚህ ከነጻነት በኃላ የታገልኩበትን በክብር አገኛለሁ፡፡

 

ለዚህ ነው ከትግሉ የሚሸሹ፣ በሌላው ሰው ደም፣ እነሱ ነፃ ለመውጣት የሚመኙ፣ ማወቅ የሚገባቸው ማንም የተለየ ደም የለውምና ትግሉን በመቀላቀል የውዴታ ግዴታ እንዳለበት ማወቅ ይገባዋል፡፡ በወያኔ ባንዳነት፣ ሰላይነት፣ በኢህአዴግ ካድሬነት፣ ተላላኪነት ጥቅማቸውን የሚያስጠብቁ ዜጎች ህዝባዊውን ትግል በሰዓቱ እንዲቀላቀሉ ጥሪ ቀርቦላቸዎል፡፡ የትግሉን አቅጣጫ፣የትግሉን አጀንዳ የሚያስቀይሩ የወያኔ የፖለቲካ ሰላዩች፣ የፖለቲካ ከፋፋዬች፣ ስም አጥፊዎች፣ከዛሬ በኃላ ቦታ አይኖራቸውም፡፡ የትግላችን ዋነኛ አጀንዳ መሬታችንን ማስመለስ ነው፣ ሁሉም በአካባቢው የጎበዝ አለቃ እየመረጠ መሬቱን፣ ዘርቶ የሚያፈራ ወርቃማ አፈሩን፣ የእምዬ ኢትዩጵያን መሬት በአርበኝነት ጠብቀው ላቆዩን አርበኞች እኛ ልጆቻቸው ለመጠበቅ ለእራሳችን ስንል ቃል እንገባለን፡፡ በየ አህጉራቱ ተሰደው በግፍ የሚኖሩ ኢትዩጵያዊያን በያሉበት ቀበቶቸውንና መቀነታቸውን አጥብቀው ህዝባዊውን እንቢተኝነትና ተጋድሎ በመደገፍ በእውቀትም በገንዘቡም፣ በሰው ኃይልም በተለይ የሠራዊቱ አባል የነበሩ ትግሉን በመቀላቀል ታሪካዊ ግዴታችሁን ለመወጣት ቆርጦ መነሳት ይኖርብናል፡፡ ‹‹በውኑ ኢትዩጵያዊ መልኩን፣ወይስ ነብር ዥንጉርጉርነቱን ሊለውጥ ይችላልን›› እንደተባለው ሁላችንም በዘር ሳንከፋፈል፣ በሃይማኖት ሳንለያይ በአንድ ቀስት አንድ ኢላማ በመምታት የቆሰለውን ወያኔና ቻይና መደምሰስ የግዜው አንገብጋቢ ጥያቄ ነው፡፡ የሜርሮክ ወርቅ የ20 አመት ኮንትራት ውል አብቅቶል የለገደንቢን የወርቅ ኃብታችንን እናስመልስ፣ የመተከል የወርቅ ኃብታችንን እናስመልስ፣ የወያኔን የኢዛና ወርቅ ሃብታችንን እናስመልስ፣ ድህነትን ምንቀርፈው የወርቅ ማዕድናችንን ስናመልስ ብቻ ነው፡፡ ‹‹ትግላችን አህያውን ፈርቶ ዳውላውን›› እንዳይሆን ደሃውን ኢትዩጵያዊ ዜጋ ከክልሌ ውጣ ከምንባባል የወርቅ ኃብታችንን ማስመለስ የጀግንነትና የአርበኝነት ተግባር ነው፡፡ በወያኔ የተነጠቅንውን የከተማና የገጠር መሬት በማስመለስ አገራችንን እንጠብቅ፣ ውስጥ ውስጡን በድብቅ እንደራጅ፣ ህዝባዊውን የአርበኞች ትግል እንቀላቀል፣ ወጣቶች በስደት በባህር ከመስመጥ ይልቅ፣ ለነፃነት፣ ለእኩልነት፣ ለዲሞክራሲ  በክብር መታገል ታሪካዊ ኃላፊነታችሁ ነው፡፡ የቀጣዩ ዘመን አገር ተረካቢ ትውልድ ወጣቶች ናችሁና፣ ነጻነት በትግል የሚገኝ እንጂ በችሮታ የሚገኝ አይደለምና ታሪክ ለመስራት ቆርታችሁ ተነሱ፡፡

 

ኢትዩጵያዊያን ዜጎች በየሰላማዊ ሠልፉ ብዙ እህትና ወንድሞቻችንን ተነጥቀናል፣ በወያኔ አጋዚ ጥይት ሞተዋል፣ ቆስለዋል፣ ታስረዋል፣ ታሪክ አይረሳችሁም ልጆቻቸው ለተሰው ወላጆች አስፈላጊውን ድጋፍ፣ የቤት፣ የመሬትና የጡረታ የደም ካሣ እንዲያገኙ ቀጣዩ የሽግግር መንግሥት ሁሉን እንዲያመቻች በህዝብ ስም እነጠይቃለን፡፡ ከዚህ ቀን በኃላ በሰላማዊ ሠልፍ ዜጋዎቻችን መገበር አይኖርብንም፣ በቤት ውስጥ የመቀመት አድማና በመሳሰሉት፣ በጎበዝ አለቃ በመምረጥ ጫካ በመግባት መታገል ብቸኛ የትግል አቅጣጫ ሆኖልና፣ለትግል ቆርጦ መነሳት ክብርና ሞገስ ያለው ሥራ ሆኖል፡፡ ሚዛኑ ያጋደለ ቀን አርበኛው ወጣት በለስ የቀናው ቀን፣የኦሮሞው፣ የአማራው፣  ጋምቤላው፣የቤኒ-ሻንጉሉ፣ የትግራዩ፣ የደቡቡ፣የአፋሩ የአርበኞች ህብረት ፈጥረው በድል አድራጊነት ወያኔን መንግለው የሚጥሉበት ቀን ቀርቦል፡፡ የነጻነት ትግሉ በሁሉም አቅጣጫ ተቀጣጥሎል፡፡ የወያኔ የመከላከያ ሠራዊትና የፖሊስ ኃይል ህዝባዊውን ትግል በመቀላቀል ታሪክ ሥራ፡፡ የህወኃት/ኢህአዴግ የፖለቲካ ካድሬዎች በግዜው ህዝባዊ ኃይሉን ተቀላቀሉ፣ በሃገራችን ብዙ ደም ፈሶልና ተጨማሪ የደም መፋሰስና የማያባራ ጦርነት የህዝብ እልቂትና የንብረት ውድመትና ጥፋት፣ የህዝብ ስደት፣ስለሚያስከትል ለህዝብ ስትሉ፣ለእውነት ስትሉ፣ለሞራልና ስነምግባራችሁ ስትሉ የገማውን ወያኔ ስርዓት ጥላችሁ ህዝባዊውን ትግል ብትቀላቀሉ፣ በክብርና በማእረግ እጃችንን ዘርግተን እንቀበላችሆላን፡፡ ይህ የአገር ጉዳይ እንጂ የቂም በቀል፣ ያልሰለጠነ የፖለቲካ ዘመን አይደለም፡፡ ሃገራችን እንደ ሲሪያ ፣የመን፣ ሱማሌ፣ደቡብ ሱዳን፣ ወዘተ እንድትሆን አንመኝምና ይቅር ለእግዜብሄር የመባባል ባህላዊ ዕሴታችን ዘላለም ይከበራል፡፡ በዚህ የወንድማማቶች ጦርነት ወደን አልገባንም፣ የጥያቄው ዋነኛ አጀንዳው የነፃነትና የባርነት፣ ከመሬትችን የመተከልና የመነቀል፣ የአንደኛ ደረጃ ዜግነትና የሁለተኛ ደረጃ ዜግነት፣የልጅና የእንጀራ ልጅ፣ የህሊናና የሆድ አደርነት፣ ጉዳይ ሆኖብን ተጋጨን እንጂ ሌላ ምን ጠብ አለንና፡፡ ስለዚህ ድሉ ቀን ተቃርቦልና ህዝባዊውን ትግል በግዜው ተቀላቀሉ፣የድል አጥቢያ አርበኛ ከመሆን ያድናችሁ፡፡

ኢኮኖውን ካላወቁ ፖለቲካውን አይነቀንቁ!!! የወያኔን የኢኮኖሚ አከርካሬ መምታት አስፈላጊ ነው!!! የከተማና ገጠር መሬታችንን እናስመልስ!!!

የወያኔ ፋሽስታዊ ‹የአስቸኮይ ጊዜ አዋጅ!› ይነሳ!!! ያለ ኢኮኖሚ ነፃነት የፖለቲካ ነፃነት የለም!!!

የኢትዩጵያ መከላከያ ሠራዊት አፈሙዝህን ወደ ወያኔ አዙር!!!  የህሊና እስረኞች ይፈቱ!!!

በወያኔ እስር ቤቶች ውስጥ ኢስብዓዊ ግርፋትና ማሰቃየት ይቁም!!!

በወያኔ እስር ቤቶች ውስጥ ኢስብአዊ የወሲብ ጥቃት ይቁም!!!

የወያኔ እስር ቤቶች በዓለም ዓቀፍ ስብአዊ መብት ኮሚሽን ይጎብኙ!!!