አርብ ምሽት የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለስድስት ወራት የሚቆይ መሆኑን የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ አስታወቁ::
የሚኒስትሮች ምክር ቤትም ውሳኔውን በሙሉ ድምፅ እንደተቀበለውና: በሃገሪቱ ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት የሽግግር መንግሥት ማቋቋም አስፈላጊ እንዳልሆነ ሚኒስትሩ ተናግረዋል::
በሃገሪቱ ያለው የፀጥታ ችግር እየተባባሰ መሆኑን ዛሬ ቅዳሜ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የተናገሩት ሚኒስትሩ ችግሩ በዋና ከተማዋ በአዲስ አበባም መንፀባረቁን ገልፀዋል::
ሚኒስትሩ እንዳሉት ኢህአዴግ ለ17 ቀናት ባደረገው ግምገማ ላይ ያለው ችግር በ15 ቀናት ውስጥ ካልተፈታ የአስቸኳይ ጊዜ ሊታወጅ እንደሚችል ቀደም ሲል ከስምምነት ላይ ተደርሶ እንደነበር ጠቁመዋል::
ለስድስት ወራት የሚቆየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በየጊዜው የሚገመገም ሲሆን አስፈላጊ ሆኖ ከተገፕ ለአራት ወራት ሊራዘም እንደሚችልም ተገልጿል::
አዋጁ በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚቀርብ የተናገሩት ሚኒስትር ሲራጅ: የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የሚከታተል ኮማንድ ፖስት ተቋቁሟል::
ምንጭ – ቢቢሲ/አማርኛ