November 5, 2019

Source: https://amharaonline.org

አቶ ደመቀ መኮንን የውሸት ሪፖርት አንሰማም! አሉ

ዛሬ የፌዴራል ዐቃቢ-ህግ ስለ ሰኔ 15 ቱ ግድያ በቤተ መንግስት ሪፖርት ሊያቀርብ ሲል በከፍተኛ ተቃውመው እንዳይቀርብ ያስደረጉት ም/ጠ/ሚ ደመቀ መኮንን:-

ግድያን ና ዘር ማጥፋትን በይፋ የፈፀሙትን ጃዋርን ና ግብረ አበሮቹን በቁጥጥር ስር አውለን ለህግ ሳናቀርብ የአደባባይ ሚስጥር ለሆነው የሰኔ 15ቱ የአመራሮቻችን ሞት በዚህ ሰዓት የውሸት ሪፖርት የምንሰማበት ሀቅሙም ሞራሉም የለንም!!

ህዛባችን በእኛ ያለው እምነት ተሸርሽሯል፣እውነት ብናወራም ማመን አቁሟል፣ ለውጡ ሲመጣ ህወሀት ያሰራቸውን ከእስር ፈትተን ከእንግዲህ ሳናጣራ አናስርም ብለን በአደባባይ ቀባጥረን በማግስቱ ብሄር-ተኮር የጅምላ እስራት ያውም በጥርጣሬ ብቻ እየፈፀምን ነው። የህዝቡን ሰላም ና ደህንነት ማስጠበቅ ባለመቻላችን ዜጎች በኖሩበት ሀገር እንደ እንስሳ በአደባባይ እየታረዱ ነው።

የሰኔ 15ቱ ግድያም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የመጀመርያ ተጠያቂዎቹ እኛው የኢትዮጵያ መንግስት ከከፍተኛ እስከ ዝቅተኛ ያለን አመራሮች ነን! ንፁሀንን በመወንጀልና በእነሱ በማላከክ እኛን ከተጠያቂነት ለመዳን የምናደርገውን የውሸት ሪፖርት ማውራት ለጊዜው ምስኪኑን ህዝብ እናታልለው ይሆናል እንጂ ከህሊናችን
ና ከታሪክ መደበቅ ግን ፈፅሞ አይታሰብም!!